አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 2 ፣ 2006 (ኤፍ.ቢ.ሲ.) በኢትዮጵያ እየተካሄዱ ያሉት የነዳጅና የተፈጥሮ ጋዝ ፍለጋዎች ተስፋ ሰጪ ምልክቶች እየታዩባቸው መሆኑን የኢፌዴሪ የማዕድን ሚኒስቴር ገለፀ።
የማእድን ሚኒስትሩ አቶ ቶሎሳ ሻጊ እንዳሉት፥ በፍለጋዎቹ እየተገኙ ያሉት መረጃዎች የነዳጅ እና የተፈጥሮ ጋዝ ሀብቶች እንደሚገኙ የሚጠቁሙና ተስፋ ሰጪዎች ናቸው።
የክምችት መጠንን በተመለከተም የተገኙት መረጃዎች እንዲሁ መልካም ውጤት ሊገኝ እንደሚችል የሚያሳዩ ናቸው ብለዋል።
በአሁኑ ወቅት 13 ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች የነዳጅ ፍለጋ ፈቃድ አውጥተው እየሰሩ መሆናቸውን የጠቆሙት ሚኒስትሩ፥ ሁለቱ ቀጥታ ወደ ቁፏሮ ገብተው የክምችት መጠኑን በማጥናት ላይ ይገኛሉ ነው ያሉት።
ቀሪዎቹ የመሬት ላይ ጥናት በማድረግ ላይ ሲሆኑ በቅርቡም ወደ ቁፋሮ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በደቡብ ኦሞ ቁፋሮ እያካሄደ የሚገኘው አፍሪካ ኦይል እስካሁን በአከባቢው እስከ 2 ሺህ 850 ሜትር ጥልቀት ያለው ጉድጓድ በመቆፈር የክምችት መጠኑን እያጠና እንደሚገኝ ነው አፍሪካ ሪቪው የዘገበው።
የማእድን ሚኒስትሩ አቶ ቶሎሳ ሻጊ እንዳሉት፥ በፍለጋዎቹ እየተገኙ ያሉት መረጃዎች የነዳጅ እና የተፈጥሮ ጋዝ ሀብቶች እንደሚገኙ የሚጠቁሙና ተስፋ ሰጪዎች ናቸው።
የክምችት መጠንን በተመለከተም የተገኙት መረጃዎች እንዲሁ መልካም ውጤት ሊገኝ እንደሚችል የሚያሳዩ ናቸው ብለዋል።
በአሁኑ ወቅት 13 ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች የነዳጅ ፍለጋ ፈቃድ አውጥተው እየሰሩ መሆናቸውን የጠቆሙት ሚኒስትሩ፥ ሁለቱ ቀጥታ ወደ ቁፏሮ ገብተው የክምችት መጠኑን በማጥናት ላይ ይገኛሉ ነው ያሉት።
ቀሪዎቹ የመሬት ላይ ጥናት በማድረግ ላይ ሲሆኑ በቅርቡም ወደ ቁፋሮ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በደቡብ ኦሞ ቁፋሮ እያካሄደ የሚገኘው አፍሪካ ኦይል እስካሁን በአከባቢው እስከ 2 ሺህ 850 ሜትር ጥልቀት ያለው ጉድጓድ በመቆፈር የክምችት መጠኑን እያጠና እንደሚገኝ ነው አፍሪካ ሪቪው የዘገበው።
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ