ሐሙስ 13 ማርች 2014

ፓስተሩ ሴቶች ፓንት እና ጡት መያዣ እንዳያደርጉ አገዱ

በ ናይሮቢ ኬንያ የሚገኘው ሎርድስ ፕሮፔለር ሪዴምሽን ቸርች ፓስተር የሆኑት ሬቨረንድ ንጆሂ፣ ወደሳቸው ቸርች የሚመጡ ሴቶች ፓንት እና ጡት መያዣ እንዳያደርጉ አገዱ፡፡
“ሰው ቤተ ክርስቲያን ሲመጣ ነጻ መሆን አለበት” ያሉት ፓስተሩ፣ ከእግዚአብሔር ጋር ለመቀራረብና መንፈስ ቅዱስም በውስጣቸው እንዲገባ ፓንትና ጡት መያዣ አድርገው መጨናነቅ የለባቸውም ስለዚህ በኔ ቸርች ይህ ታግዷል” ማለታቸውን ናይጄሪያን ዎች፣ ኬንያን ፖስት እና ሌሎችም ጋዜጦች የካቲት 24 (ማርች 3) ዘግበዋል። አንዳንዶች ይህን ተግባር የመጨረሻው ዘመን ምልክት ሲሉ ተቃውመውታል።
ከአንድ ወር በፊትም እዚህ አሜሪካ፣ ቨርጂኒያ የሚገኘው ዋይት ቴል ጸሎት ቤት፣ የራቁት አምልኮ መጀመሩንና እዚያ የሚመጡ ሁሉ ራቁታቸው መሆን እንደሚችሉ ማስታወቁን እንዲያውም ፓስተሩ፣ ፓስተር አለን ራሳቸው ሙሉ በሙሉ ራቁታቸውን ሆነው እንደሚሰብኩ በአሜሪካ ሚዲያዎች መዘገቡ የሚታወስ ነው።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ