ሐሙስ 13 ማርች 2014

የመከላከያ ሰራዊት የሎጂስቲክ መምሪያ ኃላፊ ቤታቸው ሞተው ተገኙ

ፖሊስ የአሟሟታቸውን መንስኤ አጣራለሁ ብሏል
ሰላም ገረመው
የመከላከያ ሰራዊት የሎጂስቲክ መምሪያ ኃላፊ የነበሩት ሌተናል ኮሎኔል ተ/ሚካኤል ተስፋይ በመኖሪያ ቤታቸው ውስጥ ሞተው መገኘታቸውን ፖሊስ
ጠቆመ፡፡ ሌተናል ኮሎኔሉ መደበኛ ስራቸውን አከናውነው ወደ ቤታቸው ከገቡ በኋላ ከልጆቻቸው ጋር እራትበልተው መተኛታቸውን ምንጮች ገልፀው፤ ሌሊት ላይ ድምፅ እንዳሰሙና ልጆቻቸው ደርሰው ሲያዩዋቸው ሞተው መገኘታቸውን ተናግረዋል፡፡
ጎረቤቶች ተደናግጠው ኮሎኔሉን ወደ ጦር ሃይሎች ሆስፒታል ቢወስዷቸውም ህይወታቸው ቀድሞ በማለፉ የጦር ሃይሎች ሆስፒታል የኮሎኔሉን አስክሬን በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አማካኝነት ለምርመራ ወደ ምኒልክ ሆስፒታል ልኳል፡፡
ሌተናል ኮሎኔል ተ/ሚካኤል ተስፋይ እድሜያቸው ለአቅም አዳም ካልደረሰ ሁለት ልጆቻቸው ጋር ይኖሩ እንደነበረ የታወቀ ሲሆን ባለቤታቸው በአገር ውስጥ እንደሌሉ ተጠቁሟል፡፡ ፖሊስ የኮሎኔሉን የሞት መንስኤ ለማጣራት የህክምና ምርመራ ውጤት እየተጠባበቀ መሆኑን ገልጿል፡፡

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ